ዕምነታችን

“ሁሉን በያዘ ሰማይንና ምድርን የሚታይና የማይታየውን በፈጠረ በአንድ አምላክ በእግዚአብሔር እናምናለን።

ዓለም ሳይፈጠር ከርሱ ጋር በነበረ የአብ አንድ ልጁ በሚሆን በአንድ ጌታ   በኢየሱስ ክርስቶስም እናምናለን።

ከብርሃን የተገኘ ብርሃን፣ ከእውነተኛ አምላክ የተገኘ አምላክ፤ የተፈጠረ ያይደል የተወለደ፤ በመለኮቱ ከአብ ጋር የሚተካከል።

ሁሉ በርሱ የሆነ ያለ እርሱ ግን ምንም የሆነ የለም። በሰማይም ያለ በምድርም ያለ።

ስለእኛ ስለሰው ስለ መዳኛችን ከሰማይ ወረደ። ከመንፈስ ቅዱስ የተነሣ ከቅድስት ማርያም ፈጽሞ ሰው ሆነ።

ሰው ሆኖ በጰንጤናዊ በጲላጦስ ዘመን ስለእኛ ተሰቀለ። ታመመ፤ ሞተ፤ ተቀበረም፤ በሦስተኛውም ቀን ከሙታን ተለይቶ ተነሣ፤ በቅዱሳት መጽሐፍት እንደ ተጻፈ።

በክብር ወደ ሰማይ ዐረገ፤ በአባቱም ቀኝ ተቀመጠ። ዳግመኛ ሕያዋንን ሙታንንም ይገዛ ዘንድ በጌትነት ይመጣል። ለመንግሥስቱም ፍጻሜ የለውም።

ጌታ ማሕየዊ በሚሆን ከአብ በሠረፀ በመንፈስ ቅዱስም እናምናለን። እንሰግድለት እናመሰግነውም ዘንድ፤ ከአብና ከወልድ ጋር በነብያት የተነገረ።

ከሁሉ በላይ በምትሆን ሐዋርያት በሰበሰብዋት በአንዲት ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም እናምናለን።

ኃጥያትን ለማስተሥረይ በአንዲት ጥምቀት አናምናለን።

የሙታንንም መነሣት ተስፋ እናደርጋለን የሚመጣውንም ሕይወት ለዘላለሙ አሜን።”

 

Like all Christians, Orthodox Ethiopians believe in the Holy Trinity (səllasé) of the Father, Son and Holy Spirit. We also observe typical Orthodox rituals and practices – the Feast of Epiphany (Timkat) and the Eucharist being the most important celebration and ceremonies.

To communicate the spiritual riches of ancient Christianity as found within the living local traditions of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church throughout the world...

Ethiopian Orthodox believers are strict Trinitarians,[42] maintaining the Orthodox teaching that God is united in three persons: Father, Son, and Holy Spirit. This concept is known as səllasé (ሥላሴ),[citation needed] Ge'ez for "Trinity".

Daily services constitute only a small part of an Ethiopian Orthodox Christian's religious observance. Several holy days require prolonged services, singing and dancing, and feasting

Miaphysitism holds that in the one person of Jesus Christ, divinity and humanity are united in one (μία, mia) nature (φύσις - "physis") without separation, without confusion, without alteration and without mixing where Christ is consubstantial with God the Father.[10] Around 500 bishops within the patriarchates of AlexandriaAntioch and Jerusalem refused to accept the dyophysitism (two natures) doctrine decreed by the Council of Chalcedon in 451, an incident that resulted in the second major split in the main body of the state church of the Roman Empire.[

ሥርዓተ ጸሎት ወስግደት ዘሰሙነ ሕማማት

አኮቴተ ቁርባን ዘጎርጎርዮሰ የሆሳዕና ቅዳሴ

4251 E Broadway Blvd, Tucson, AZ 85711, USA Copyright © 2022. All rights reserved Ethiopian Orthodox Tewahedo Church

ጥንተ ስቅለት- መጋቢት 27

ጥንተ ስቅለት- መጋቢት 27፣ 34 ዓ.ም.
የዛሬ አንድ ሺሕ ዘጠኝ መቶ ሰባ አምስት ዓመት በዕለተ ዓርብ መጋቢት 27 ቀን 34 ዓመተ ምሕረት (5534 ዓመተ ዓለም) የክብር ባለቤት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ዓለም ድኅነት በሥጋ የተሰቀለበት ዕለት ነው፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ እንደተጻፈው፡ ‹‹ከስድስት ሰዓት ጀምሮም እስከ ዘጠኝ ሰዓት ዓለም ሁሉ ጨለማ ሆነ›› (ማቴዎስ 27፡45) ፈጣሪዋ በዕንጨት መስቀል ላይ ተሰቅሎ ባየችው ጊዜ ፀሐይ ጨለመች፡፡ እርሱም ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም የነሣትን ለባዊት ነባቢት የሆነች ነፍሱን ከሥጋው ለያት፡፡ ሐዋርያጴጥሮስ በሥጋ ምውት ሲሆን በመለኮት ሕያው ነው እንዳለ፤ ነፍሱ ከመለኮት ሳትለይ ከሥጋ ተለየች፤ በዚያ ጊዜ ሥጋ ከመለኮት ሳይለይ በዕንጨት መስቀል ላይ ተሰቅሎ ነበር፡፡ እንዲሁም ነፍስ ከመለኮት ጋር አንድ ሁና እሥረኞች ነፍሳትን ትፈታቸው ዘንድ ወደ ሲኦል ወረደች፡፡ (1 ጴጥሮስ 3፡18-19)

Early Crucifixion of the world savior,

Early Crucifixion- March 27, ETC  34 AD.
One thousand nine hundred and seventy-five years ago today, Friday, March 27, 34th year of mercy (5534 years of the world) is the day when our glorious Lord and Savior Jesus Christ was crucified for the salvation of the world.  As written in the Bible: "From six o'clock until nine o'clock the whole world became dark" (Matthew 27:45).  And he separated his soul from his body, which was raised from our Lady, the Holy Virgin Mary.  Apostle Peter said that he is dead in the flesh but alive in the divine;  His soul was separated from the body without being separated from the divine.  At that time, the flesh was crucified on a wooden cross.  And the soul, becoming one with the divine, descends into hell to free the captive souls.  (1 Peter 3:18-19)

May the blessing of the cross be upon us forever. Amen

Today, you blessed our church congregation.Thanks much for being here and blessing us...!

You blessed our church congregation. **†††*በአገልግሎታችሁ ተቀድሰናል ተባርከናል።

ድኃኔ ዓለም ያክብርልን / ይስጥልን።*†††**

  1. A sample pictures and videos are listed from the event.